Mehr von Ethiopian Press Agency/Tigrigna auf Facebook anzeigen

Aktueller Beitrag der Seite
ከተለያዩ የአገሪቷ ክልሎች የተውጣጡ የአደዋ ተጓዥ ጋዜጠኞች ዛሬ አደዋ ገብተዋል
ጋዜጠኞቹ የአደዋ ተራራዎች...ን በጎበኙበት ወቅት አድዋ ዙሪያ ያሉ አርሶ አደሮች ለእንግዶቻቸው ያደረጉት ግብዣ ያሳዩት ፍቅር አስደማሚ ነበር ::
ፎቶ ዳኜ አበራ Mehr anzeigen
የመንግሥት የትራንፖርት ድርጅቶች በ2012 በጀት ግማሽ ዓመት ከታክስ በፊት ብር 9 ነጥብ 05 ቢሊዮን አተረ...ፉ
********************************************************
(ኢ.ፕ.ድ)
በመንግሥት የልማት ድርጅቶች ይዞታና አስተዳደር ኤጀንሲ ሥር በትራንስፖርት ዘርፍ የሚገኙ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ እና የኢትዮጵያ ባህር ትራንስፖርትና ሎጀስቲክስ አገልግሎት ድርጅት በ2012 በጀት የመጀመሪያው ግማሽ ዓመት በጊዚያዊ የሂሳብ መረጃ መሠረት ከታክስ በፊት በድምሩ 9 ነጥብ 05 ቢሊዮን አተረፉ፡፡
ይህ አፈጻጸም የልማት ድርጅቶቹ አቅደውት ከነበረው የብር 12 ነጥብ 38 ቢሊዮን ትርፍ አንጻር ሲታይ ክንውናቸው የዕቅዳቸውን 73 ነጥብ 12 በመቶ እንደሆነ የድርጅቶቹ አፈጻጸም በኤጀንሲው መሰብሰቢያ አዳራሽ የካቲት 11 እና 16 ቀን 2012 ዓ.ም. በተገመገመበት ወቅት ታውቋል፡፡
የግምገማ መድረኩን የኤጀንሲው ዋና ዳይሬክተር አቶ በየነ ገብረመስቀል የመሩት ሲሆን፣የየልማት ድርጅቶቹ የቦርድ ተወካዮች፣ዋና ሥራአስፈጻሚዎች፣የማኔጅመንት አባላትና እንዲሁም የኤጀንሲው የትራንስፖርት ዘርፍ ዳይሬክተር እና ባለሙያዎች በግምገማው ተሳትፈዋል፡፡
ድርጅቶቹ ይህንን ትርፍ ሊያገኙ የቻሉት የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ በዓለም አቀፍና በሀገር ውስጥ የአየር ትራንስፖርት ሰዎችና ዕቃ በማጓጓዝ፣ የኤርፖርት አገልግሎትና የሆቴል መስተንግዶ በማቅረብና እንዲሁም የአቬሽን ሥልጠና በመስጠት እና የኢትዮጵያ ባህር ትራንስፖርትና ሎጀስቲክስ አገልግሎት ድርጅት በባህርና በየብስ ገቢና ወጪ ዕቃዎችን በማጓጓዝ፣በሀገር ውስጥ ደረቅ ወደቦች ኮንቴይነርና ተሸከርካሪዎችን በማስተናገድና ሌሎች ተያያዥ የሎጀስቲክስ አገልግሎት በማከናወን በድምሩ ብር 91 ነጥብ 30 ቢሊዮን ገቢ ለማግኘት አቅደው ብር 79 ነጥብ 63 ቢሊዮን ወይም የዕቅዳቸውን 87.21 በመቶ ማግኘት በመቻላቸው ነው፡፡
ከተገኘው አጠቃላይ የብር 79 ነጥብ 63 ቢሊዮን ገቢ ከፍተኛው ብር 67 ነጥብ 83 ቢሊዮን ወይም 85 ነጥብ 18 በመቶው የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ሲሆን፣ቀሪው ብር 11 ነጥብ 79 ቢሊዮን ወይም 14 ነጥብ 81 በመቶ የኢትዮጵያ ባህር ትራንስፖርትና ሎጀስቲክስ አገልግሎት ድርጅት ነው፡፡ በተናጠል ሲታይ ግን የኢትዮጵያ ባህር ትራንስፖርትና ሎጀስቲክስ አገልግሎት ድርጅት ትርፍ አፈጻጸም ከዕቅዱ የ4 በመቶ ብልጫ አለው፡፡
በተመሳሳይ ከተገኘው ጠቅላላ የብር 9 ነጥብ 05 ትርፍ ከፍተኛውን ብር 7 ነጥብ 82 ቢሊዮን ወይም ከአጠቃላዩ 86 ነጥብ 44 በመቶ ያህል ድርሻ የያዘው የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ሲሆን፣የኢትዮጵያ ባህር ትራንስፖርትና ሎጀስቲክስ አገልግሎት ድርጅት ከአጠቃላዩ ትርፍ ብር 1 ነጥብ 23 ወይም 13 ነጥብ 55 በመቶ ድርሻ ይዟል፡፡
በግምገማው ማጠቃለያ ላይ ድርጅቶቹ በዓለም አቀፍ የአየርና የባህር ትራንስፖርት ገበያ ውስጥ ጭምር ገብተው በዋጋም ሆነ በአገልግሎት ጥራት ተወዳዳሪ ሆነው የሚሰሩ እንደመሆናቸው የግማሽ ዓመቱ አፈጻጸማቸው አበረታች በመሆኑ በቀጣዮቹ የ2012 በጀት ዓመት ቀሪ ጊዜም ይህንኑ አጠናክረው እንዲቀጥሉና ለዚህም ኤጀንሲው ተገቢውን ድጋፍ እንደሚያደርግ ተገልጾ ግምገማው መጠናቀቁን ከኤጀንሲው ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡ Mehr anzeigen
ፕሬዝዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ የኢትዮጵያ ኦሎምፒክ ቡድን የመጀመሪያው ችቦ በይፋ ለኩሰዋል
************...************************
(ኢ.ፕ.ድ)
የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ የኦሎምፒክ ቡድኑን የቶክዮ 2020 የመጀመሪያውን ችቦ ዛሬ ወዋት መስቀል አደባባይ በመገኘት በይፋ ለኩሰዋል።
ፕሬዝዳንቷ ባስተላለፉት መልዕክት “እኛ ኢትዮጵያውያን በተባባረ አንድነትና ህብረት ወደ ላቀ ብልፅግና እንደርሳለን፤ ኢትዮጵያ ብዙ ጀግኖች ታፈራለች” ብለዋል።
የኢትዮጵያ መንግስት ለኦሎምፒክ ቡድኑ ድጋፉን በኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ በኩል አሳይቷል ያሉት ፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ፥ “እኔም ባለኝ አቅም ሁሉ እደግፋለሁ” ብለዋል።
በዓለም መድረክ ላይ ሰንደቅ ዓላማችንን ከማውለብለብ ባሻገር ያስለመዳችሁንን ድል እንድታጎናፅፉን እንፈልጋለን ከዛሬዋ ቀን ጀምሮ በርትታችሁ ስሩም ብለዋል።
በስነስርዓቱ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሀላፊዎች፣ የአዲስ አበባ ነዋሪዎች፣ ስፖርተኞች ታዋቂ ሰዎች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።
የቀጣይ የችቦ ልኮሳን ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ተረክቧል፡፡
በደመቀ ሁኔታ በተካሄደው ፕሮግራም ብዙዎቹ ስፖርት በመስራት በመጨፈር ጭምር ደስታቸውን ማሳየታቸውን ከአዲስ አበባ ስፖርት ኮሚሽን የተገኘው መረጃ ያመለክታል። Mehr anzeigen
